ሲጋራ ማጨስ የሚያስከትላቸው የጤና ጠንቆች
ሲጋራ ማጨስ በአጠቃላይ የጤናችንን ሁኔታ ይጎዳል፤ በስራ፣በትምህርት እና በማኀበራዊ ሕይወታችን ላይ አሉታዊ ችግሮችን ይፈጥራል፡፡
- የልብ በሽታን ተጋላጭነት በአራት እጥፍ ይጨምራል፡፡
- የደም መርጋት በሽታ ተጋላጭነትን በአራት እጥፍ ይጨምራል፡፡
- የሳንባ ካንሰር ተጋላጭነትን በሃያ አምስት እጥፍ ይጨምራል፡፡
- የሰውነት በሽታን የመከላከል አቅምን ይቀንሳል፡፡
- የጥርስ፣ምላስ እና የአፍ በሽታዎችን ያመጣል፡፡
ሲጋራ ማጨስ በመተንፈሻ ስርአት አካሎች ላይ የሚያደርሰው ጉዳት
- የሳንባ ካንሰር ያመጣል፡፡
- የመተንፈሻ ትቦ እና ጥቃቅን ህብረ ህዋሳት በማጥበብ የማይድን የሳንባ ሕመም ያስከትላል ይህም ሕመም ለሞት ያደርሳል፡፡
- አስም ላለባቸው ሰዎች አስምን ያባብሳል በቀላል ሕክምና ለመዳን ያዳግታቸዋል፡፡
ሲጋራ ማጨስ ተጋላጭነትን የሚጨምራቸው የካንሰር አይነቶች
- የሽንት ፊኛ
- የደም
- የማሕፀን በር
- የአንጀት
- የጉሮሮ
- የኩላሊት እና የሽንት ትቦ
- የጉበት
- የአፍና ተዛማጅ የሆኑ የሰውነት አካላት
- የቆሽት እና
- የጨጓራ ካንሰር ናቸው፡፡
ሲጋራ ማጨስ በስነ ተዋልዶ ጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት
በሴቶች ላይ
- ቀኑ ያልደረሰ ልጅ መውለድ
- በማሕፀን ውስጥ የፅንስ መሞ ት
- አነስተኛ ክብደት ያለው ልጅ መውለድ
- ከማሕፀን ውጭ እርግዝና
- የፅንስ አካል ጉዳት
በወንዶች ላይ
- የወንድ የዘር ፈሳሽ መጠን መቀነስ ያስከትላል፡፡

